top of page

ለመከሩ ሰራተኞች
...የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡፡ ሉቃስ 10፡2
ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ! ማርቆስ 16፡15
በዓለማችን ከሚገኙ 7 ቢሊዮን ህዝብ መሀል ቢያንስ 3.17 ቢሊዮን ገደማ የሚሆነው የኢንተርኔት ተጠቃሚ እንደሆነ ያውቃሉ? ምን ያህሉ ህዝብ ድኖ ይሆን ? እንዴትስ ነው የወንጌልን መልዕክት የምናደርሳቸው ?
ልክ ከመቶ በጎች መካከል የጠፋውን ለመፈለግ እንዳስኬደው ፍቅር በዘመናችን የጠፉብንን ወገኖች ለመፈለግ ጸጋ እና ተነሳሽነት ያስፈልገናል፡፡
ዓላማችን ፡- ወንጌልን በድረ-ገጾቸ፣ በኢ-ሜይል፣ በፌስቡክ፣ በጉግል ፕላስ ፣ በቲውተር፣ በስልክ፣ በቫይበር ላይ መልዕክቶችን በመላክ መመስከር ነው፡፡
እያንዳንዳችን ጓደኞቻችንን፣ ቤተሰባችንን፣ ጎረቤታችንን ...የምናድንበት ዕድል እንዳያልፈን እንትጋ!!!
ለምስክርነት የሚረዳንን አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ በዚህ ድህረ ገጽ ውስጥ ልናገኝ እንችላለን፡፡ ስልጠና ሲፈልጉ ደግሞ በአድራሻችን ይጻፉልን፡፡
ሁላችን ለወንጌል እንኑር ፤ ያለንንም ለወንጌል እናኑር!

GlobeWithBible

ReachTheLost

TheOnlyDoor

GlobeWithBible
1/3
bottom of page

